በ2030 ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኅብረት ሥራ ማኅበር ሆኖ ማየት.

ራዕይ
በ2030 ዓለም ዓቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኅብረት ሥራ ማኅበር ሆኖ ማየት
ተልዕኮ
አባላትን በማስተባበር ተገቢውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በፍላጎት ላይ የተመሰረተ በሃገራችን የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ላይ አስተዋፅኦ በማበርከት ለአባላት የተሻለ የቁጠባ የብድር እና ሌሎች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ በማድረግ የኑሮ ደረጃቸውን ማሻሻል፡፡
ዓላማ
- አባላት የቁጠባ ባህላቸውን እንዲያሳድጉ በማድረግ በተመጣጣኝ ወለድ የብድር የሚያገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸት
- የተለያዩ የሥራ ፈጠራና የንግድ ክህሎት ስልጠናዎችን በመስጠት የአባላትንና የሌሎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም እንዲያሳድጉ ማስቻል
- አባላት የአካባቢ ልማትን ፣ አየር ንብረትን እና የመልካም አስተዳደር ገፅታን የሚገነባ ሥራ ላይ እንዲሰማሩ ማበረታታት
- ለሴቶች እና ወጣቶች የስራ ዕድልን በመፍጠር በድህነት ቅነሳ ላይ የራስን የድርሻን መወጣት